የፈለግኩትን መኪና 25% ቆጥቤ፣ ቀሪውን ተደራሽ አሟልቶልኛል፤ እርስዎም ይምጡና የዚህ ስኬት ተካፋይ ይሁኑ።
ያሬድ ደቦጭ እባላለሁ፤ እዚህ አዲስ አበባ ነኝ። በኮንስትራክሽን ስራ ላይ ነው የምተዳደረው። ስለ ተደራሽ መጀመሪያ የሰማሁት በፌስቡክ ነበረ፤ ከዚያ በኋላ ፒያሳ በሚገኘው ቢሮአቸው በመሄድ መረጃዎችን ወሰድኩ። በዚያውም ቁጠባ ጀመርኩኝ። አቀባበላቸው በጣም ደስ የሚልና ቤተሰባዊነት የሚሰማው ነው። መግዛት የፈለግኩትን መኪና 25% ቆጥቤ፣ ቀሪውን ተደራሽ አሟልቶልኛል። እርስዎም ይምጡ፣ እንደ እኔ የተደራሽ ቤተሰብ ይሁኑ፤ መኪና በመግዛት፣ ትንሽ ቆጥበው ትልቅ ይሁኑ!